መግቢያ።

መግቢያ።

     ''እኔ፡ ኢትዮጵያዊ፥ ኢትዮጵያዊት፥ ወይም፡ የእግዚአብሔር ሰው ነኝ!'' የሚል ወገን ኹሉ፡ ከዓርባ ዓመታት በላይ፡ ይኽው፡ ያለማቋረጥ እየተሠቃየበት ላለው በሽታ፡ ኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት፡ ''ወእግዚአብሔር ውእቱ ቃል''''ቃልም፡ እግዚአብሔር ነው'' የተባለለትን፡ የወልደ አብወእም፡ ማለትም፡ የእግዚአብሔር አብና የእግዚአብሔር እም (ድንግል ማርያም) ልጅ፡ የመሲሕ ኢየሱስን ሕያውና ዘለዓለማዊ ቃል፡ ይኽው፡ ለሚሠቃይበት በሽታው፡ ዘለዓለማዊ መፍትሔና አማናዊ መድኃኒት ይኾነው ዘንድ፡ ''ዘቦ ዕዝን፡ ሰሚዐ ለይስማዕ!''''የሚሰማ ጆሮ ያለው፡ መስማትን፡ ይስማ!''፥ እንዲሁም፡ ''ኵሎ ዘይቤለክሙ ግበሩ!''"ልጄ ወዳጄ፡ የሚላችሁን ኹሉ፡ ስሙት! አድርጉት! ፈጽሙትም!" እያለች፡ እነኚህን፡ ከታች የሰፈሩትን፡ የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን መልእክታት፡ በአዋጅ መልክ ሠርጋና አዘጋጅታ አቅርባላችኋለችና፥ እናንት፡ እውነትን የተራባችሁና የተጠማችሁ፡ መሳሕያትና መሳሕያን ዕድምተኞቿ፡ ይህን፡ መለኮታዊ የድምፅ ጥሪዋን ሰምታችሁ፥ በእግዚአብሔር እውነትና በመንፈስ ቅዱስ አምልኮም ኾናችሁ፡ ''ሰማያዊ ምግቧን፡ ትመገቡት ዘንድ ይኹን!'' በማለት፡ በእግዚአብሔር ስም ታሳስባችኋለች።