ኪዳናዊ አክሊለ-ጊዮርጊስ፡ ስለትክክለኛውና ስለእውነተኛው የምድር ቅርጽ በተመለከተ ለላከልን የእ-ጦማር ጥያቄ፡ የተሰጠ መልስ።

ከኪዳናዊ አክሊለ-ጊዮርጊስ፡ የደረሰን እጦማር፦

+ዮም ፍሥሓ ኮነ!
በእንተ ፍልሰታ፡ ውስተ አርያም!
ለእግዚአብሔር እም፡ ድንግል ማርያም!+

     ጤናውን ይስጥልኝ፣ በእግዚኣብሔር መንግሥት፣ ኪዳናውያትና ኪዳናውያን እኅቶቼና ወንድሞቼ! እንደምን ኣላችሁልኝ!?
     ቤተሰቤና እኔ፣ በቸሩ ፈጣሪ እርዳታ፣ በፍጹም መልካም ሕይወት እንገኛለን፤ ምስጋናችሁ ዛሬም ይድረሳቸውና።
በዚህች እ-ጦማሬ ላስተላልፍ የፈለግኁትን ኣስተያየትና የሃሳብ ጥቆማ- የኪዳናዊ ጋሽዬ ኤርሚያስ ከበደ ቃለ መጠይቅ ሥዕላዊ መጽሔትን በተመለከተ- ሥዕላዊ መጽሔቱን ስመለከት፡ ገና ከመነሻው ላይ በተመለከትኩት፣ እንደእኔ እምነት ግን ትክክለኛ ኣይደለም ብዬ በያዝኩት፣ የምንኖርባትን ዓለም ሥዕላዊ መግለጫ ወይም የቅርፅና ሕልውና ጉዳያን በተመለከተ ነው።

ሙሉ የጥያቄና መልስ ክንውኑን ለመከታተል፡ እንደሚከተለው ይቀጥሉ!...