ሐምሌ ፲፰፡ ፪ሺ፯ ዓ.ም. (25 July 2015)

ከዮሓንስ ኢትዮጲስ ለቀረቡ ጥያቄዎች፡ ከንቡረ እድ ኤርምያስ ከበደ ወ.ኢ. የተሰጡ መልሶች፥ ከእንግሊዝኛው ወደኢትዮጵያኛ፡ በኪዳናዊ ዮሴፍ ጥላኹን የተተረጎመው ተከውኖ።

ኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት፡

ተደብቀው የኖሩ፡ አዳዲስ ምሥጢራትን የገለጠችባቸው፣

ከዮሓንስ ኢትዮጲስ ለቀረቡ፡
ተከታታይ ጥያቄዎች፡ የተሰጡ መልሶች።
 
ኪዳናዊ ዮሴፍ ጥላኹን፡
ከእንግሊዝኛው ዝግጅት፡ ወደኢትዮጵያኛው እንደተረጐመው፤

አብርሆትና አርትዖት፡ በኪዳናዊ ኤርምያስ ከበደ ወልደ-ኢየሱስ (ንቡረ-እድ)

+   +   +

ከዮሓንስ ኢትዮጲስ፡ ለኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት የቀረበ፡ ፩ደኛ ጥያቄ፡-

     ኢየሱስ፡ ኢትዮጵያዊ ስለመኾኑ፡ ማረጋገጫዎ ምን እንደኾነ ልጠይቅዎ ግድ ይለኛል? የትኛው መጽሓፍ ቅዱስ፡ ይህን ይናገራል? ኢየሱስ፡ ኢትዮጵያዊ ከኾነ፣ "የጥንቶቹ አይሁድ፡ ከኢትዮጵያውያን ጋር፡ በአካል ተመሳሳይ ነበሩ፤" ማለት ነው?

ኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት፡ የሰጠችው መልስ፡-