ቍጥር ፭/፳፻፮ ዓ. ም. ቃለ-ዐዋድ።

ቍጥር ፭/፳፻፮ ዓ. ም. ቃለ-ዐዋድ።

ቃለ ዐዋድ!
እምኢትዮጵያ፡ ዘመንግሥተ እግዚአብሔር።

የአዋጅ ቃል!
ከኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት።

ስለአምልኳችን ያለን እውቀትና የአፈጻጸሙ ሥርዓት ትክክለኛ ስለመኾኑ በተመለከተ።

ስለሰንበትና ስለስግደት፥ ስለድንግል ማርያምና ስለቅዱሱ ኪዳን ተልእኮ፡
ኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት፡ በቅዱሱ ኪዳን፡ የኢትዮጵያዊነት ተዋሕዶ ሃይማኖቷ መሠረት፡ አጽንታ ያኖረችው ምግባራዊ ሥርዓቷ፡ ምን እንደኾነ፡ በግልጽና በትክክል ሊታወቅ ይገባል።

ሰንበትን በሚመለከት፦
"ሰንበት"፡ ጥንትም፥ እስከዛሬና ዛሬም፥ ለዘለዓለምም፡ አንዲት ናት፤ ኹለት ሰንበታት የሉም። ያች አንዲቷ ሰንበት፦ በቀዳማዊው የፍጥረት ዘመን፡"እግዚአብሔርም፡ ሰባተኛዋን ቀን ባረካት፤ ቀደሳትም፤ የጀመረውን የመፍጠር ሥራውን ኹሉ ፈጽሞ፡ በእርሷ ዐርፎባታልና።" የተባለችው ናት፤