ቍጥር ፮/፳፻፮ ዓ. ም. ቃለ-ዐዋድ።

ቍጥር ፮/፳፻፮ ዓ. ም. ቃለ-ዐዋድ።

ቃለ ዐዋድ!
እምኢትዮጵያ፡ ዘመንግሥተ እግዚአብሔር።

የአዋጅ ቃል!
ከኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት።

የድንግል ማርያም ክብርዋ፡ እስከየት ድረስ ነው?

'የድንግል ማርያም ክብርዋ፡ እስከየት ድረስ ነው?'' የሚለውን ቍም ነገር፡ ቅዱስ ያሬድ፡ በድጓው የዜማ ድርሰቱ፡ 'ወይቤላ እግዚአብሔር ለማርያም፦ 'አዝማንየ አዝማንኪ፣ አምጣንየ አምጣንኪ፣ ማርያም ሐቀፍኪዮ ወአነ ዮም ወለድክዎ!' ማለትም፡ «እግዚአብሔርም፡ ማርያምን እንዲህ አላት፦ "የባሕርዬ ዘመን፡ ዘመንሽ ነው፤ የአካሌም መጠን፡ መጠንሽ ነው። ስለዚህ፡ እኔ ዛሬ የወለድሁትን ልጄን፡ አንቺ ማርያም አቀፍሽው!"»