ኢየሱስ ክርስቶስ፥ ኢትዮጵያዊነት። መጋቢት ፯ ቀን፡ ፪ሺ፱ ዓ.ም. (16 March 2017)

ለኪዳናዊ አንዱ-ዓለም ደብዳቤ የተሰጠ መልስ።

ዮም ፍሥሓ ኮነ!
በእንተ ተዝካረ-ጾሙ ለእግዚእነ ኢየሱስ መሲሕ!

ይድረስ፦ በቅዱሱ ኪዳን ለተወደድኸው ወንድሜና የአገልግሎት ባልደረባዬ፡ ኪዳናዊ አንዱዓለም!

በተወደደችው እኅታችንና የክህነት ባልደረባችን፡ በኪዳናዊት ኂሩት አማካይነት የላክህልኝ፣ ደኅንነትህን ያበሠረኝና መልካካም ቃላትን፣ አማናዊዉንና ተአምራዊዉን ሕልምህንም የያዘው፡ የምሥራች እ-ጦማርህ ደረሰኝ፤ እግዚአብሔር ይስጥልኝ።

በአንተ በኩል እየተላለፈ፡ ለእኔም የሚደርሰኝ፡ በእየጊዜው፡ ወደአንተ የሚመጣው መለኮታዊ መልእክት፡ ለአንተ ብቻ ሳይኾን፡ ለኹላችንም ኪዳናውያንና ኪዳናውያት ሃይማኖትና ምግባር፥ አምልኮና ሕይወት ማጽኛ እንዲኾን፡ ሰማያውያኑና ዘለዓለማውያኑ ወላጆቻችን፡ እግዚአብሔር አብ እና እግዝእተብሔር እም ድንግል ማርያም የሚልኩልን ስለኾነ...

ከኪዳናዊ አንዱ-ዓለም የደረሰን ደብዳቤ።

ይድረስ፦ ለተወደድከው ኪዳናዊው ጋሽዬ፡ በያለንበት በመልካም የምታኖረንንና የምትመግበንን፡ ቸሪቱንና ደጊቱን፡ ኢትዮጵያ የእግዚአብሔር መንግሥትን፡ ከነልጅዋ ከመድሃኒዓለም ጋር እያመሰገንሁ፡ ኪዳናዊ የወንድምነት ሰላምታዬን፡ ለኪዳናዊው ቤተሰብህ ጭምር አቀርብልሃለሁ።
በመቀጠልም፡ ከዚህ በፊት የምሥራች እንደምልህ ሁሉ፡ ዛሬም በዕለተ መድሃኒዓለም የምሥራች ልልህ እወዳለሁ።

በ፳፬/፫/፳፻፱ ዓ.ም. በዕለተ ቅዳሜ ያየሁት ሕልም ነው።