ኦ ማርያም እምነ ዘበሰማያት

የኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት፡ የ"አቡነ ዘበሰማያት"ን እና የ"ኦ ማርያም እምነ ዘበሰማያት"ን ጸሎታት፡ በተመለከተ፡ ለደረሱን፡ የነቀፌታ ትችቶችና መጠይቃውያን አስተያየቶች፡ የተሰጠ መልስ።

ይድረስ፦ ለአቶ ብንያም ምሕረት!
     ኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት፡ "ዮም ፍሥሓ ኮነ! በእንተ ርደተ መንፈስ ቅዱስ ላዕለ ኵላ ምድር፡ ዘኢትዮጵያ፡ መንግሥተ እግዚአብሔር!" እያለች፡ ሰላምታዋንና የእግዚአብሔር እውነት የኾነችውን፡ ኢትዮጵያዊት መልእክቷን፡ በእናትነት ፍቅር፡ እንዲህ በማስቀደም ታቀርብልዎታለች።
     በፌስቡክ መድረካችን ላይ፡ ስለጻፉልን ትችት፡ "እግዜር ይስጥልን!"