ግንቦት ፲፮ ቀን፥ ፳፻፯ ዓ.ም. (24 May 2015)

ስለታቦተ ጽዮን የተላለፈ፡ የእግዚአብሔር መልእክት።

ከኪዳናዊ ኃይለ ማርያም፡ በእንግሊዝኛ ተጽፎ የደረሰን መልእክት።

ከኪዳናዊ ንቡረ-እድ ኤርምያስ ከበደ ወልደ-ኢየሱስ የተሰጠ ሓተታ።

ዮም ፍሥሓ ኮነ!
በእንተ ርደተ መንፈስ ቅዱስ ላዕለ ሓዋርያት፡
በጽርሓ ጽዮን ቅድስት!

የመስከረም ለቺሳ፡ ''ዩቶፕያ (Utopia)'' የሚለው፡ የሰር ቶማስ ሞር መጽሓፍ፡ ኢትዮጵያኛ የትርጉም ሥራና የምርምር ማስታወሻዎች።

ይድረስ፦ ለኪዳናውያትና ለኪዳናውያን የኢትዮጵያ ልጆች! ለሌሎቻችሁም፡ የምንባብ ታዳሚዎቻችን ኹሉ!

እኔ፡ ኪዳናዊ ወንድማችሁ፡ ንቡረ-እድ ኤርምያስ ከበደ ወልደ-ኢየሱስ፡ ኢትዮጵያዊ ሰላምታዬን፡ በያላችሁበት፡ በእግዚአብሔር ስም አቀርብላችኋለሁ!

"ለእንግሊዝ መንግሥታዊና ሃይማኖታዊ ተሓድሶ፡ ምክንያት የኾነው፡ የመካከለኛው ዘመን፡ የኢትዮጵያ ሥርዓተ መንግሥትና የሕዝቧ አኗኗር -  (ኢ) ዩቶፕያ - የትርጕም ሥራና የምርምር ማስታወሻዎች - እውነተኛው "ሕዳሴ" ወይም "ተሓድሶ"፡ ከምንታዌነት (Dualism)፡ ወደተዋሕዶ (Unity) የሚደረግ፡ ኹሉን አቀፍ ኅብረተሰባዊ የንስሓ ጕዞ መኾኑን የሚያሳይ፡ ተጨባጭ እና ታሪካዊ ማስረጃ" በሚል አርእስት፡ በኪዳናዊት መስከረም ለቺሣ ተደርሶ፡ በ፳፻፮ ዓመተ ምሕረት የታተመውንና በሥርጭት ላይ የሚገኘውን መጽሓፍ አነበብሁት።