ቅድስት ሥላሴ። ጥር ፰ ቀን፥ ፳፻፯ ዓ.ም. (January 16 2015)

በፌስ ቡክ የኅዋ መድረካችን፡ ከአቶ ዞሚ ስንቱ የቀረበ ጥያቄና ለዚያ ጥያቄ የሰጠነው ምላሽ።

በፌስ ቡክ የኅዋ መድረካችን፡ ከአቶ "ዞሚ ስንቱ" ለቀረበልን ጥያቄ፡ በዚያው የኅዋ መድረክ፡ የሰጠነውን መንፈስ ቅዱሳዊ ምላሽ፡ ለእናንተ፡ የኅዋ ሰሌዳ አንባቢዎቻችንና ተከታታዮቻችን፡ እንደሚከተለው አቅርበንላችኋልና በተለመደው የጥሞና መንፈስ ኹናችሁ ተከተታተሉት።

ከአቶ ዞሚ ስንቱ የቀረበ ጥያቄ፦

    ቃለ ሕይወት ያሰማልን! በመቀጠልም፡ ኹለት ጥያቄዎች አሉኝ።
    ፩. "በዚህም እውነታ፡ "ድንግል ማርያም፡ ከፍጥረተ ዓለሙ አስቀድሞ፡ በቅድስት ሥላሴነቷ፡ የሦስቱም አንድነት መገኛ እንደነበረች ኹሉ፡..." ሲል፡ ምን ማለት ነው? አልገባኝም።
    ፪. ኢየሱስ ክርስቶስ፡ ከድንግል የተፀነሰው፡ ታኅሣሥ ፩ ከኾነ፥ ልደቱ፡ ከ፱ ወር በላይ አልፎ፡ እንዴት ታኅሣሥ ፳፱ ሊኾን ቻለ? በዚህ አቈጣጠር፡ ፲፪ ወር ከ፳፱ ቀን አይኾንም? እግዚአብሔር ይስጥልኝ።