ቍጥር ፫/፳፻፮ ዓ. ም. ቃለ-ዐዋድ።

ቃለ ዐዋድ!
እምኢትዮጵያ፡ ዘመንግሥተ እግዚአብሔር።

የአዋጅ ቃል!
ከኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት።

ስለግእዝ ምንነትና ማንነት።

ኪዳናውያንና ኪዳናውያት የቅዱስ ኪዳኗ ኢትዮጵያ ልጆች! ስለግእዝ ምንነትና ማንነት፡ በሚበቃ አውቃችኋል። ከዚህ እውቀታችሁ የተነሣ፡ በሰብኣዊው ተፈጥሮአችን፡ የዘር ግንዳችን የኾኑት፡ አዳም እና ሔዋን፡ ከፈጣሪያቸውና ከአምላካቸው ከእግዚአብሔር ያገኙትና እርሱ፡ ከእነርሱ፥ እነርሱም፡ ከእርሱ ጋር፥ እርስ በእርሳቸውም ይነጋገሩበት የነበረው: የመጀመሪያው የሰው ልጆች ቋንቋ፡ ግእዝ መኾኑን ተገንዝባችኋል።

ከዚህ ግንዛቤያችሁም የተነሣ፡ በፍጥረት የልደት ዘመን፡ "ወአሐዱ ነገሩ፡ ለኵሉ ዓለም፤ ወአሐዱ ቃሉ።" ማለትም፡ "የሰው ኹሉ ቋንቋው አንድ፥ አነጋገሩም፡ አንድ ነበር።" ተብሎ፡ በቅዱሳት መጻሕፍት ተመዝግቦ የሚዘከረው፡ ያ አንድ ቋንቋ፥ ያ አንድ ንግግር፡ ግእዝ መኾኑን፡ በእምነት ተቀብላችኋል።

ኖኅና ሚስቱ ሓይከል፥ ሦስቱ ልጆቻቸው፡ ሴም፥ ካም፥ ያፌት እና ሦስቱ ሚስቶቻቸው፡ ምድርን፡ ከጥፋቷና ከርኵሰቷ ሊያጸዳት ካጥለቀለቃት የውኃ ሙላት የዳኑባት መርከብ ባረፈችበት መሬት ላይ በማኅበረሰብነት መኖር ከጀመሩ በኋላ፡ ወልደውና በጋብቻ ተዋልደው፡ እየበዙ ከኼዱም በኋላ፡ ዓለሙን ተከፋፍለው እስከተበታተኑበት ጊዜ ድረስ፡ ይነጋገሩበት የነበረው ቋንቋቸው፡ ይኸው ግእዝ እንደነበረ አረጋግጣችኋል። (ዘፍጥ. ፲፩፥ ፩።)

ከዚህ የሚከተሉት ሰባት እውነታዎች፡ የግእዝን ምንነትና ማንነት፡ በአዎንታዊ መልኩ፡ በቀላሉና በግልጽ አስረግጠው፡ በአጽንዖት ያስረዳሉ፦

መልእክቱን፡ በሙሉ ለመከታተል፡ እንደሚከትለው ይቀጥሉ!...