Faith Ethiopic

እኛ፡ የኢትዮጵያ ልጆች፦

አንድ አምላክ በሚኾን፡ በአሸናፊው እግዚአብሔር  እናምናለን። 

እርሱም፡ ኹሉን የያዘው፣ ሰማይንና ምድርን፥ የሚታየውንና የማይታየውንም የፈጠረው ነው።

አንድ አምላክ የኾነው፡ አሸናፊው እግዚአብሔር፡ ይህን አንድነቱን፡ እርሱ በሠራው፡ በመለኮታዊው የጋብቻ ሥርዓት፡ በእግዚአብሔር አብእም ኹለትነት፡ ፍጹም እንዳደረገው እናምናለን።

የእግዚአብሔር አንድነትና ሦስትነት፡ የአሸናፊው እግዚአብሔር ቅድስት ሥላሴ ዙፋንና የእግዚአብሔር መንግሥት ኢትዮጵያ በኾነችው፡ በእግዝእተብሔር እም፡ ድንግል ማርያም፡ የተዋሕዶ አኗኗርና አካል እንደተገለጠ እናምናለን።

ዓለም ሳይፈጠር፡ ከእርሱ ጋራ በነበረ፥ አንድ የእግዚአብሔር አብእም ልጅ፥ አንድ ጌታ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር ወልድም እናምናለን።

እኛ፡ የኢትዮጵያ ልጆች፦

እግዚአብሔር፡ ለሰው ልጆች፣ ለወንዶቹም፥ ለሴቶቹም፣ የሰጣቸውን ቃል ኪዳናት፡ ጠብቆ በኖረው፡ በቅዱሱ ኪዳን ኢትዮጵያዊነታችን እናምናለን።

አምላካችን፡ ይህን የኢትዮጵያዊ እና የኢትዮጵያዊት ሕያው ሰውነት፡ በመጀመሪያው የፍጥረት ዘመን፡ በአዳምና ሔዋን ሥርዓተ ጋብቻ፡ በኪዳነ ልቦና መሠረተው፤

ከዚያም፡ በኖኅ ቀስተ ደመና፥ በመልከ ጼዴቅ ቍርባን እና በአብርሃም ግርዛት፡ ገንብቶ አሳደገው፤

በመካከለኛውም የሕግ ዘመን፡ በሙሴ ጽላትና በዳዊት ዙፋን አዋቅሮ፥ የኢትዮጵያዊቷን ንግሥት፡ የማክዳንና የእስራኤላዊዉን ንጉሥ፡ የሰሎሞንን የዘር ሓረጎች በማዋሓድ፡ በኪዳነ ኦሪት አከናወነው፤

አባታችንና እናታችን፥ እኅታችንና ወንድማችን፥ መንፈሳችንም፡ እግዚአብሔር ሆይ!

አቤቱ እንቀድስሃለን እናመሰግንሃለንም፤ አቤቱ እናወድስሃለን፤ እንታመንብሃለን፤ አቤቱ እናገንሃለንም፤ ለቅዱስ ስምህ እንታዘዛለን፣ እንሰግድልሃለን፤ ጕልበት ኹሉ፡ ለአንተ ይሰግዳል፤ አንደበትም ኹሉ፡ ወደአንተ ይጮሃል።

አንተ፡ የአማልክት አምላክ ነህ፤ የገዢዎች ገዢ ነህ፤ የንጉሦችም ንጉሥ ነህ። አንተ፡ የሥጋዊው ኹሉ፥ የነፍሳዊዉም ኹሉ ወገን ፈጣሪ ነህ።

ልጅህ እግዚአብሔር ወልድ፡ ኢየሱስ መሲሕ፡ "እናንተ ስትጸልዩ፡

እናታችንና መድኃኒታችን እግዝእተብሔር ማርያም ሆይ!

በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል ሰላምታ፡ "ሰላም!" እንልሻለን።

በመንፈስሽ እና በነፍስሽ፣ በሥጋሽም፡ ድንግል ነሽ። በዚህ የንጽሕና ባሕርይሽ፡ የአሸናፊው የእግዚአብሔር እናት ነሽና፡ ይህ ሰላምታ፡ ለአንቺ ይገባል።

ማሕፀንሽ፡ የሕይወት ዛፍ ፍሬ የኾነውን፡ ቅዱሱን አዳም ስላስገኘ፣ አንቺ፡ ከሴቶች ኹሉ ተለይተሽ የተባረክሽ፡ ቅድስቲቱ ሔዋን ነሽ። ቀድሞ በነቢያት፡ "ኢትዮጵያ፡ እጆቿን፡ ወደእግዚአብሔር ታደርሳለች!"  የተባልሽ፥ እኛም፡ "እናታችን ጽዮን!" ስንልሽ የኖርን፡ በሰማይና በምድር ንግሥታችን ሆይ! ደስ ይበልሽ! እግዚአብሔር፡ አንቺን፡ የመዳናችን ምክንያት አድርጎ፡ ኪዳነ ምሕረቱን፡ ለዘለዓለም ፈጽሟልና፡ "ጸጋን የተመላሽ ሆይ! ብፅዕት ነሽ!" እያልን፡ ዘወትር እናመሰግንሻለን።