ቍጥር ፬/፳፻፮ ዓ. ም. ቃለ-ዐዋድ።

ቃለ ዐዋድ!
እምኢትዮጵያ፡ ዘመንግሥተ እግዚአብሔር።

የአዋጅ ቃል!
ከኢትዮጵያ፡ የእግዚአብሔር መንግሥት።

ስለሰላምታ አሰጣጣችን ሥርዓት በተመለከተ።
ኪዳናውያንና ኪዳናውያት የኾኑት የቀደሙት ወላጆቻችን፡ "እጃችሁን ለማንም አትስጡ! አትማረኩ!" ብለው በማስጠንቀቅ፡ "እጅ ንሡ!" ያሉበትን፡ የቅዱሱን ኪዳን የሰላምታ አሰጣጣችንን ሥርዓት፡ ኹላችንም የምናውቀው ነው።

ይኹን እንጂ፡"እጅ ንሡ!" ማለት፡ እንደመማረክ የሚያስቈጥረውን፡ "እጃችሁን፡ ለሰላምታም ቢኾን፡ አስቀድማችሁ ዘርግታችሁ፡ ለሌላ አትስጡ!" ማለት እንጂ፡ "ሌላው፡ በራሱ ፈቃደኛነት፡ እጁን፡ ለወዳጅነት ሰላምታ፡ አስቀድሞ ዘርግቶ ቢሰጣችሁ፡ አትጨብጡት!" ማለት አለመኾኑን ተረድተን፡ በዚሁ መሠረት መፈጸሙ፡ አግባብ ይኾናል።

መልእክቱን፡ በሙሉ ለመከታተል፡ እንደሚከተለው ይቀጥሉ!...