የኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያውያት የሃይማኖት ጸሎት።

የኢትዮጵያ: የሃይማኖት ጸሎት።

እኛ፡ የኢትዮጵያ ልጆች፦

አንድ አምላክ በሚኾን፡ በአሸናፊው እግዚአብሔር  እናምናለን። 

እርሱም፡ ኹሉን የያዘው፣ ሰማይንና ምድርን፥ የሚታየውንና የማይታየውንም የፈጠረው ነው።

አንድ አምላክ የኾነው፡ አሸናፊው እግዚአብሔር፡ ይህን አንድነቱን፡ እርሱ በሠራው፡ በመለኮታዊው የጋብቻ ሥርዓት፡ በእግዚአብሔር አብእም ኹለትነት፡ ፍጹም እንዳደረገው እናምናለን።

የእግዚአብሔር አንድነትና ሦስትነት፡ የአሸናፊው እግዚአብሔር ቅድስት ሥላሴ ዙፋንና የእግዚአብሔር መንግሥት ኢትዮጵያ በኾነችው፡ በእግዝእተብሔር እም፡ ድንግል ማርያም፡ የተዋሕዶ አኗኗርና አካል እንደተገለጠ እናምናለን።

ዓለም ሳይፈጠር፡ ከእርሱ ጋራ በነበረ፥ አንድ የእግዚአብሔር አብእም ልጅ፥ አንድ ጌታ በሚኾን፡ በእግዚአብሔር ወልድም እናምናለን።